ለሙያ ብቃት ማረጋገጫ ምዘና(COC) አገልግሎት ፈላጊዎች በሙሉ:-

የአገና ኮንስትራክሽንና ኢንደስትሪያል ኮሌጅ በ2016 በጀት ዓመት ለ2ኛ ዙር የሙያ ብቃት ምዘና አገልግሎት የምዝገባ ፕሮግራም ከነሀሴ 15-24/2015 ድረስ መመዝገብ ትችላላችሁ።በመሆኑም የምዘና አገልግሎት ለማግኘት መመዝገብ የምትፈልጉ አጫጭር ስልጠና ሰልጣኞች/የግል ተመዛኞች በሙሉ የሚከተሉትን መረጃዎች በሟሟላት መቅረብ ይጠበቅባችኋል:-

1. የዲግሪ/ዲፕሎማ ሰርተፊኬት ኮፒ
2. ማንነታችሁ የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ እና ሁለት/2/ ጉርድ ፎቶ-ግራፍ
3. ከደረጃ-1 በላይ ተመዛኞች ከምዘና ደረጃው በታች ያሉ የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ኮፒ
4. ለብቃት ምዘናው የተፈቀደ ክፍያ ብር በንግድ ባንክ አካውንት ቁ. 1000168288248 የተከፈለበት ደረሰኝ በምዝገባ ወቅት ማሟላት ግዴታ ነው።

✍️ማሳሰቢያ:- #1. ለአካውንቲንግ፣ ለማኔጅመንት እና ለHNS/Database ተመዛኞች ብቁ እንድትሆኑ(ምዘናውን እንድታልፉ) የሚያግዙ የተለያዩ ፈተናዎችንና መልመጃዎች ከምዘና ፕሮግራም ሶስት ቀናት አስቀድሞ በነጻ ክለሳ የሚሰጥ መሆኑን ከወዲሁ እንገልጻለን፡፡

2.በምዘናው ዕለት ከኮሌጁ የተሰጠ የፈተና አዳራሽ መግቢያ ስሊፕ፣ ማንነታችሁን በግልጽ የሚገልፅ የቀበሌ/የኮሌጁ መታወቂያ፣ አንድ 4X3 የሆነ ጉርድ ፎቶግራፍ መሉ ስምና የሙያ ዓይነትና ደረጃ የተጻፈበት መያዥ ይጠበቅባችኋል፡፡

Recent