ለሙያ ብቃት ማረጋገጫ ምዘና(COC) አገልግሎት ፈላጊዎች በሙሉ:-

የአገና ኮንስትራክሽንና ኢንደስትሪያል ኮሌጅ በ2016 በጀት ዓመት ለ1ኛ ዙር የሙያ ብቃት ምዘና አገልግሎት የምዝገባ ፕሮግራም ከሐምሌ 03/2015 ጀምሮ ይጀምራል።በመሆኑም የምዘና አገልግሎት ለማግኘት መመዝገብ የምትፈልጉ መደበኛ/የግል ተመዛኞች በሙሉ እስከ ሐምሌ 14/2015 ድረስ የሚከተሉትን መረጃዎች አሟልታችሁ መቅረብ ይጠበቅባችኋል:-

1. የዲግሪ/ዲፕሎማ ሰርተፊኬት ኮፒ እና ኦርጅናል
2. ማንነታችሁ የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ እና ሁለት/2/ ጉርድ ፎቶ-ግራፍ
3. ከደረጃ-1 በላይ ተመዛኞች ከምዘና ደረጃው በታች ያሉ የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት
4. ለብቃት ምዘናው የተፈቀደ ክፍያ ብር በንግድ ባንክ አካውንት ቁ. የተከፈለበት ደረሰኝ በምዝገባ ወቅት ማሟላት ግዴታ ነው።

✍️ማሳሰቢያ:-
በምዘናው ዕለት ተመዛኞች የሚከተሉትን ጉዳዮች በጥንቃቄ መፈጸም ይጠበቅባቸዋል:-

1. ከኮሌጁ የተሰጠ የፈተና አዳራሽ መግቢያ ስሊፕ
2. ማንነታችሁን በግልጽ የሚገልፅ የቀበሌ/የኮሌጁ መታወቂያ
3. አንድ 4X3 የሆነ ጉርድ ፎቶግራፍ መሉ ስምና የሙያ ዓይነትና ደረጃ የተጻፈበት
4. በዕለቱ ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት የኮሌጁ ጊቢ ውስጥ  ተፈትሾ መግባት
5. ምንም ዓይነት ልብስ ወይም ሌሎች ቁሶች በቦርሳ ይዞ መግባት የተከለከለ ነው!!
6. ለሌሎች ተመዛኞች ተክቶ መመዘን:ሰነድ ማጭበርበር ወይም ሌላ መንኛው የምዘና አሰራር መጣስ በወንጀል የሚያስቀጣ መሆኑን መረዳት እና ተገቢውን መመሪያ መተግበር ያስፈልጋል።

Recent